­

ትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ

ሃይማኖት ፤ ሃይመነ አሳመነ ፡ ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ፤ ትርጉሙም በአንድ አምላክ ማመን ለአንድ አምላክ መታመን ማለትን ይገልጻል ። “ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደተፈጠሩ የሚታየውም ከማይታየው እንደሆነ እናውቃለን። ዕብራውያን  11፥ 3 በዓይናችን ለምናየው ለግዙፉ ዓለምና ለማይታየው ለረቂቁ ዓለም ፈጠሪ አስገኝ መጋቢ አለው ፤ እሱም እግዚአብሔር ነው ብሎ ማመን የሃይማኖት መጀመሪያ ነው። የሃይማኖት ትምሕርት፤ የሚነገረው

By |May 8th, 2016|Categories: ትምሕርተ ሃይማኖት, ጽሁፍ|0 Comments

ምሥጢረ ቀንዲል

ቀንዲል (ቅብዓ ቅዱስ) በመጽሐፍ ቅዱስ ዘይት እተተባለ ይጠራል። የሚጋጀውም ከንጹህ ወይራ ዘይት ሲሆን ፤ ህሙማነ ሥጋና ህሙማነ ነፍስ እየተቀቡ የሚፈወሱበት የተቀደሰ ቅባት ነው ። በዚህም የተቀደሰ ቅባት በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ ሰዎች በሚታመሙ ጊዜ ፡ እየተቀቡ ይፈወሱበት ነበር ። ኢሳ 1 ፥ 6 ። ሉቃ 10 ፥ 34 ። በሐዲስ ኪዳንም ሐዋርያት ህሙማነ ሥጋንና ህሙማነ

ምሥጢረ ተክሊል

ተክሊል ከለለ ፤ ጋረደ ። ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ተክሊል ማለት ፤ መከለል ፣ መወሰን ፣ መጋረድ ፣ መለየት ፣ ማለት ሲሆን  በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ለሚጋቡ ምዕማናን የሚፈጸምላቸው ሥርዓት ነው። እግዚአብሔር ወንድና ሴት አድርጎ ከፈጠራቸው በኋላ ምድርን ሙሏት ብሎ አዘዛቸው።(ዘፍ 1 ፥ 27)  ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ሴትና ወንድ በጋብቻ እየተሳሰሩ ልጆችን በመውለድ መባዛት ጀመሩ

ምሥጢረ ክህነት

ካህን ፦ ተክህነ አገለገለ ። ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ፤ ካህን ማለት የእግዚአብሔር አገልጋይ ፤ የምዕመናን አባት ፤ ጠባቂ ፤ መጋቢ ማለት ነው ። ምሥጢረ ክህነት በብሉይ ኪዳን የክህነት አንዱ መገለጫው መስዋዕት ማቅረብ ሲሆን ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዚህ አገልግሎት የተመረጠውና ካህን ተብሎ የተጠራው መልከ ጼዴቅ ነው ። ዘፍ 14፥18 ። በኋላም እግዚአብሔር በቃል ኪዳኑ

ምሥጢረ ንስሐ

ንስሐ ፦ ነስሐ ተፀፀተ ካለው የተገኘ ሲሆን ፤ ንስሐ ማለት በሠሩት ኃጢአት መፀፀት ፣ ማዘን ፣ ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ መወሰን ማለት ነው። ንስሐ ከዘለዓለማዊ ፍርድ የሚያድን ፤ ዘማዊውን እንደ ድንግል ፤ ሌባውን መጽዋች የሚያደርግ በፊት ከተሠራው ኃጢአት ንጹህ አድርጎ ፤ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ የሚያደርግ ምሥጢር ነው ። ከንስሐ በፊት መፀፀት አንድ ክርስቲያን በድፍረትም ይሁን በስህተት

ምሥጢረ ሜሮን

ሜሮን ቅባት ማለት ሲሆን ለመንፈሳዊ አገልግሎት ብቻ የሚውል የተቀደሰ ቅባት ነው ። የተለያየ መዓዛ ከሚሰጡ ዕፀዋት ተቀምሞና ተነጥሮ ይዘጋጃል ። በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ ካህናት የሚሾሙት ፤ ነገሥታት የሚግሡት ፤ የተቀደሰ ቅብዓ ክህነትናቅብዓ መንግሥት እየተቀቡ ነበር ። ዘፀ 28፥41 ። ዘፀ 29፥7 ፤ ዘሌ 4፥3 ። ዘሌ 6፥20 ። ዘሌ 8፥2 ። 1ሳሙ 9፥16 ።

ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን

1  የጌታችን ትንሣኤ ስለ ጌታችን ሞትና ትንሣኤ የተነገረ ትንቢት ፤ የተመሰለ ምሳሌ ትንቢት እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁ ፤ እግዚአብሔር (እግዚአብሔርነቴ) ደግፎኛልና ነቃሁ ። መዝ 3 ፥ 5 ። እግዚአብሔር ይነሣ ፤ ጠላቶቹም ይበተኑ ፤ የሚጠሉትም ከፊቱ ይሽሹ ። መዝ 27 ፥ 1 ። እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሳ ። መዝ 77 ፥ 65 ። ምሳሌ ዮናስ ፤

ምሥጢረ ቁርባን

ቁርባን ፤ ማለት ፣ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ አምኃ ፣ መስዋዕት ፣ መንፈሳዊ ነገር ሁሉ ማለት ሲሆን ፤ በዚህ ትምሕርታችን ግን ፤ ስለ ሐዲስ ኪዳን መስዋዕት (የክርስቶስ ሥጋና ደም) እንማራለን ። በብሉይ ኪዳን ለሐዲስ ኪዳን ቁርባን (መስዋዕት) ምሳሌዎች የመልከ ጼዴቅ መስዋዕት ዘፍ 14 ፥ 18 ። ዕብ 5 ፥ 6 ። ዕብ 6 ፥ 1

ምሥጢረ ሥጋዌ

ሥጋዌ : ተሰገወ ሰው ሆነ ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን : ምሥጢረ ሥጋዌ ማለት ሰው የመሆን ምሥጢር ማለት ነው:: አምላክ ለምን ሰው ሆነ? 1. አዳምን ከበደል ሊያነጻው አዳም የሰይጣንን ምክር በመስማት እግዚብአሔር አትብላ ያለውን ዕፀ በለስ በልቶ ትእዛዙን በማፍረሱ ከፈጣሪው በተጣላ ጊዜ የሞት ፍርድ (ሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ) ተፈረደበት ። ዘፍ 3፥1 ። ለጥፋቱ ምክንያት