አምድ ማለት ምሰሶ ማለት ሲሆን አእማድ ማለት ምሰሶዎች ማለት ነው ። ቤት በአምድ (በኮለም) እንደሚፀና ፤ ሃይማኖትም በነዚህ ምሥጢራት ተጠቃሎ ይገለጻል ፤ ምዕመናንም እነዚህን ምሥጢራት በመማር ፀንተው ይኖራሉ ።
ምሥጢር ፤ ማለት ለተወሰነ ጊዜ በተወሰኑ ሰዎች ብቻ ተጠብቆ የሚቆይ ሲሆን ፤ በዚህ ትምህርታችን ግን በሚታዩ ምሳሌዎች የማይታየውን የሃይማኖት ምሥጢር መረዳት ፤ በሚታይ አገልግሎት የማይታይ ፀጋ ማግኘት ማለት ነው ።
አምስት ፤ ቁጥራቸው አምስት ብቻ ሆኖ የተወሰነው ፤ በ1 ሳሙ 17 ፥ 40 ። እና በ 1ቆሮ 14 ፥ 19 ። ባለው ቃል መሠረት ሲሆን ፤ አምስት መሆናቸውና የተደረጉባቸው ድንቅ ሥራዎች የአምስቱ አእማደ ምሥጢር ምሳሌነታቸውን ያስረዳል
ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን
1 የጌታችን ትንሣኤ ስለ ጌታችን ሞትና ትንሣኤ የተነገረ ትንቢት ፤ የተመሰለ ምሳሌ ትንቢት እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁ ፤ እግዚአብሔር (እግዚአብሔርነቴ) ደግፎኛልና ነቃሁ ። መዝ 3 ፥ 5 ። እግዚአብሔር ይነሣ ፤ ጠላቶቹም ይበተኑ ፤ የሚጠሉትም ከፊቱ
ምሥጢረ ቁርባን
ቁርባን ፤ ማለት ፣ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ አምኃ ፣ መስዋዕት ፣ መንፈሳዊ ነገር ሁሉ ማለት ሲሆን ፤ በዚህ ትምሕርታችን ግን ፤ ስለ ሐዲስ ኪዳን መስዋዕት (የክርስቶስ ሥጋና ደም) እንማራለን ። በብሉይ ኪዳን ለሐዲስ ኪዳን
ምሥጢረ ሥጋዌ
ሥጋዌ : ተሰገወ ሰው ሆነ ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን : ምሥጢረ ሥጋዌ ማለት ሰው የመሆን ምሥጢር ማለት ነው:: አምላክ ለምን ሰው ሆነ? 1. አዳምን ከበደል ሊያነጻው አዳም የሰይጣንን ምክር በመስማት እግዚብአሔር አትብላ ያለውን ዕፀ
ምሥጢረ ሥላሴ
ሠለሰ ሶስት አደረገ ፤ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ፤ ሥላሴ ማለት ሶስትነት ማለት ነው ። በዚህ ትምህርት የአምላክን አንድነት ሶስትነት እንማራለን ። የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በምንማርበት ጊዜ ከሂሳብ ቀመር ህግ አስተሳሰብ ውጭ ሆነን ነው
Leave A Comment