ምሥጢረ ቀንዲል

ምሥጢረ ቀንዲል

ምሥጢረ ቀንዲል

ቀንዲል (ቅብዓ ቅዱስ) በመጽሐፍ ቅዱስ ዘይት እተተባለ ይጠራል። የሚጋጀውም ከንጹህ ወይራ ዘይት ሲሆን ፤ ህሙማነ ሥጋና ህሙማነ ነፍስ እየተቀቡ የሚፈወሱበት የተቀደሰ ቅባት ነው ።

በዚህም የተቀደሰ ቅባት በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ ሰዎች በሚታመሙ ጊዜ ፡ እየተቀቡ ይፈወሱበት ነበር ። ኢሳ 1 ፥ 6 ። ሉቃ 10 ፥ 34 ።

በሐዲስ ኪዳንም ሐዋርያት ህሙማነ ሥጋንና ህሙማነ ነፍስን ቅብዓ ቅዱስ እየቀቡ ከነበረባቸው ደዌ ፈውሰዋቸዋል ። ማር 6 ፥ 13 ። በቀጣይም ፡ ምዕመናን በሚታመሙበት ጊዜ ፤ ካህናት እንዲጸልዩላቸውና ቅብዓ ቅዱስ ቀብተው እንዲፈውሷቸው ታዝዘዋል። (ያዕ 5 ፥ 14)

የቅብዓ ቅዱስ ጥቅም

ቅብዓ ቅዱስ በማንኛውም ዓይነት በሽታ በተለይ በቁስል ለተመቱና ጆሯቸው ለታመመባቸው ሰዎች ፤ እንዲሁም ደዌ ነፍስ ላደረባቸውና ረድኤተ እግዚአብሔር አጋዥ እንዲሆናቸው ፣ ከኃጢአታቸውም እንዲነጹ የፈለጉ ምዕመናን ፤ ካህኑ ጸሎተ ቀንዲል ጸልዮ በሚቀባቸው ጊዜ ከነበረባቸው የሥጋና በሽታና የነፍስ ደዌ (ኃጢአት) ይፈወሳሉ ። ነገር ግን በሚቀቡበት ጊዜ እግዚአብሔር በዚህ የተቀደሰ (ዘይት) ቅብዓ ቅዱስ ላይ አድሮ ካደረባቸው ደዌ ፡እንደሚያድናቸው በፍጹም ልባቸው ማመን አለባቸው ።

ቅብዓ ቅዱስ የሚቀቡ ፤ አምነው የተጠመቁ ክርስቲያኖች ሲሆኑ ፤ ከመቀበቀታቸው በፊት ንስሐ መግባትና ራሳቸውን መቀደስ አለባቸው ። ሥርዓቱ የሚፈጸመው በካህናት ሲሆን ፤ በመጀመሪያ ጸሎቱ ቤተ ክርስቲያን ወይም ታማሚው በተኛበት ቦታ ዙሪያ ፡ ያም ባይሆን በካህኑ ጸሎት ቤት ከተጸለየበት በኋላ የታመመው (የቆሰለው) ቦታ ላይ ይቀባል ።